Jump to content

የአገው ባህል

ከWiktionary

ፊፊ፦ በአገው ብሄረሰቦች ዘንድ ተወዳጅ ባህላዊ የትንፋሽ ሙዚቃ መሳሪያ ነው። ፊፊ በጃዊ፣ዳንጉርና ቋራ ወረዳዎች ከነሀሴ አጋማሽ ጀምሮ ማታ ማታ በየሰፈሩ እየነፉ የሚጫወቱ ሲሆን በዋናነት የመስቀል በአል ማድመቂያ ነው። ፊፊ የመስቀል ዋዜማ ጀምሮ መስከረም 18 በቤተክርስትያን ታቦቱ በማጀብ በክብረ በአል መልክ ይከበራል። ፊፊ የሚሰራው ከበረሃ ቅርቀሃ ሲሆን አይነታቸውም 7(ሰባት) ናቸው። እነሱም፦ቹዋ፣ታንኬ፣ቻክቻካ፣ሳራካ፣እንፃንቲ፣ቅዛንቲ እና ዶምፔ ናቸው የመስቀል በአል ሲከበር የሚዜሙ የዜማ ስልቶች፦ጊኚ፣አጎቲኒ፣አሁባንባኒ፣ወሴዳሊ፣ይማንጃ ቲኪሊ ወዘተ ናቸው